Hiber Radio: የሕወሓት አስተዳደር ተለጣፊ አንድነት ፓርቲ መመስረቱ… የግንቦትና አርበኞች ግንባር ውህደት መነቃነቅ መፍጠሩ… ባለስልጣናቱ ለውጭ ሚዲያዎች የዋጋ ግሽበት መኖሩን ማመናቸውና ሌሎችም

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ
ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

የህብር ሬዲዮ ጥር 3 ቀን 2007 ፕሮግራም የኢሳት ኤርትራ መግባትና የአርበኞች ግንባርና የግንቦት ሰባትን ውህደት በተመለከተ ከጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና ጋር ቆይታ አድርገናል (ሙሉውን ያዳምጡ) <…ምርጫ ቦርድ በአራት ቀን ውስጥ ጊባዔ አድርጉ አለ ባልጠበቀው ሁኔታ ከመላው አገሪቱ ጉባዔተኛው መጥቶ ጉባዔው ሲደረግ በስፍራው ሳይገኝ ተለጣፊ አንድነት አቋቁሜያለሁ አለ ። ኢ/ር ግዛቸውን የመረጠው የጠቅላላ ጉባዔ አባላት መካከል ከ209 በላይ ተገኝቶ አቶ በላይ ፈቃዱን መርጧል ሕግ የለም እንጂ ሕግ ቢኖር ያ በቂ ነው ከዚህ በሁዋላ አንድነት ከሚበረከክ ቢፈርስ ይሻላል ….> አቶ አስራት አብርሃም የአንድነት ተጠባባቂ የሕዝብ ግንኙነት የነበሩ የዛሬውን የአንድነት ጉባዔና የምርጫ ቦርድን ሕገ ወጥ አካሄድ በተመለከተ ከሰጡን ማብራሪያ(ሙሉውን ያዳምጡት) በፓሪስ የተደረገው የሽብር ጥቃት፣ የመናገር ነጻነትና ተከትሎት የመጡት ጥአቄዎች(ልዩ ዘገባ) <<የሞት ጉዞ>> መጽሐፍ ደራሲ ከሆነው ጋዜጠኛና ደራሲ ግሩም ተክለሀይማኖትን ካለበት የመን እንዲሁም የ <<ምስጦቹ>> መጽሐፍ ደራሲ ተዘራ ታምራትን ከግብጽ ካይሮ ስለ መጽሐፋቸው አወያይተናል (ሙሉውን ያዳምጡት) ሌሎችም ዜናዎቻችን በኢትዮጵያ ያለው የዋጋ ግሽበት እየጨመረ መሔዱን የአገዛዙ ባለስልጣናት ለውጭ ሚዲያ አመኑ በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነው ጥንታዊው ጣይቱ ሆቴል ዛሬ በተነሳው የእሳት ቃጠሎ ከፍተኛ ውድመት ደረሰበት የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ጋና ላይ ተከስክሶ ወደቀ አንድነት ፓርቲ በአስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤው ፕሬዝዳንቱን ደግሞ መረጠ ምርጫ ቦርድና ሕውሓት በጋራ አንድነት የሚል ተለጣፊ ድርጅት ፈጥረው ፕሬዝዳንት ያሉት ተመረጠ በተለጣፊው አንድነት ምርጫ ላይ አባላት ያልሆኑና የደህንነቱ መ/ቤት ሰዎች በአካባቢው እንደነበሩ ለማወቅ ተችሏል ትንሳኤ ኢህአፓ በድርጅቱ ስም የሚንቀሳቀሱት ቡድኖች ከእርስ በእርስ ጥሎ ማለፍ ለፀረ ወያኔ ትግሉ ቅድሚያ በመስጠት ዛሬም አንድ ላይ እንዲመጡ ጠየቀ የግንቦት ሰባትና የአርበኞች ግንባር ውህደት በአገር ውስጥና በውጭ መነቃቃት እየፈጠረ ነው ሌሎችም ዜናዎች አሉ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *