Hiber Radio: አብይ ጉዳይ! ይፈቱ! ይፈቱ! ይፈቱ!

ጌታቸው ሽፈራው

ጋዜጠኛ እስክንድርን ጨምሮ መጋቢት 17/2010 ዓም 30 ሰላማዊ ሰዎች ታስረዋል። እነ እስክንድር አዲስ አበባ ላይ ለእስረኞች ምስጋና የተዘጋጀ ፕሮግራም ላይ ነው የታሰሩት። ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ አራት ቀን ሞላቸው፣ ባለፉት ሁለት ቀናት የእስር ቆይታቸው የተሻለ ነበር። ዛሬ ደግሞ አስከፊ ወደሆነው የእስር ክፍል መልሰዋቸዋል። “የኮማንድ ፖስቱን ውሳኔ እየጠበቅን ነው” እየተባለ እነሱ በአስከፊ እስር ላይ ናቸው።

ባህርዳር ላይ የታሰሩት ወጣቶች ሕጋዊ የፓርቲ ምስረታ ሰነድ ይዘው ነው። እነሱም በተመሳሳይ እስር ሁኔታ ላይ ይገኛሉ! አብዩ ጉዳይ የእነዚህ ንፁሃን መሆን አለበት!

ይፈቱ!

መጋቢት 17/2010 ዓም ከታሰሩት ጋዜጠኞች፣ ጦማሪያን፣ ፖለቲከኞች፣ እና ምሁራን መካከል:_

አዲስ አበባ

1) ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ

2)ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ

3) አቶ አንዱዓለም አራጌ

4) አቶ አዲሱ ጌታነህ

5) ጦማሪ ዘላለም ወርቅ አገኘሁ

6) ጦማሪ ማህሌት ፋንታሁን

7) ጦማሪና ጋዜጠኛ በፍቃዱ ኃይሉ

8) ወይንሸት ሞላ

9) አቶ ይድነቃቸው አዲስ

 

10) አቶ ስንታየሁ ቸኮል

11) አቶ ተፈራ ተስፋዬ

ባህርዳር

12) ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ (ባ/ዳር ዩንቨርሲቲ መምህርና የጣና ደህንነትና የአካባቢ ጥበቃ ማህበር ፕሬዚደንት እና ተመራማሪ፣ ረዳት ፕሮፊሰር)

13) ጋሻው መርሻ (የአንጸባቂው ኮከብ መጽኃፍ ከታቢ፤ አዲስ አበባ በማስተማር ሙያ ላይ ይገኛል))

14) የሱፍ ኢብራሂም (ወሎ ዩኒቨርሲቲ መምህር የነበረና በአሁንኑ ወቅት ጠበቃ)

15) ተመስገን ተሰማ (ወሎ ዩኒቨርሲቲ መምህር፤የወሎ ዩኒቨርስቲ የህግ ትምህርት ቤት መስራች፣ ረዳት ፕሮፊሰር እና አማራ ነን የሚለው መዝሙርም ገጣሚ)

16) በለጠ ሞላ ( ተባባሪ ፕሮፊሰር ፡አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሌክቸረር)

17) ጋዜጠኛ ንጋቱ አስረስ (የአማራ ቴሌቪዥን ጋዜጠኛ(አርታኢ)፤ከ1997 እስከ 1999 የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአማራ ተማሪዎች ማህበር ፕሬዜዳት፤)

18) ጋዜጠኛ በለጠ ካሳ (የቀለም ቀንድ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ የነበረ)

19)አቶ ሲሳይ አልታሰብ( ሲቪል ኢንጅነር)

20) አቶ ዳንኤል አበባው

21) አቶ መንግስቴ ተገኔ

22) አቶ ቦጋለ አራጌ

23) አቶ ካሱ ኃይሉ (የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ

መምህር፡የማህበረሰብ ሳይንስ ተመራማሪ)

24) አቶ ተሰማ ካሳሁን

25)አቶ ድርሳን ብርሃኔ

26) አቶ በሪሁን አሰፋ

27)አቶ ፍቅሩ ካሳው

28) አዲሱ መለሰ (ደ/ታቦር ዩኒቨርሲቲ መምህር)

29) አቶ ተመስገን ብርሃኑ

30) አንድ በስም ያልተጠቀሰ ግለሰብ ይገኝበታል!

ይፈቱ! ይፈቱ!

ጋዜጠኛ ጌአተቸው ሽፈራውን እናመሰግናለን።እኛም የቅርቡን ብቻ ሳይሆን ዛሬም ድረስ በእስር ላይ አሉት ሁሉም የፖለቲካና የህሊና እስረኞች ይፈቱ ምርጫው በተግባር ለውጥ ለማምታት መሰረት ለመጣል ከሆነ በተግባር ይታይ እንላለን።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *