Hiber Radio በደቡብ አፍሪካ ዛሬም ኢትዮጵያውያን የጥቃት ዒላማ መሆናቸው፣ በኬኒያ ያሉ ከ35 የሚበልጡ ኢትዮጵያውያን ጋዜጠኞች ሕይወታቸው አደጋ ላይ መሆነ፣ አሜሪካ የኢትዮጵአን ምርጫ ተከትሎ በአገሪቱ ያሉ ዜጎቿን ማስጠንቀቋ፣ ናይጄሪያዊው አገረ ገዢ ያገባሁት ኢትዮጵያዊት አይደለችም ማለታቸው፣ በኤርትራ ከሚገኘው ታጣቂ ሀይል ሊቀመንበር ጋር የተደረገ ቃለ መጠይቅ፣ የፕ/ር አስራት መታሰቢያ እና ሌሎችም

 

habtamu1

ጋዜጠኛ ሐብታሙ አሰፋ

የህብር ሬዲዮ የግንቦት 9  ቀን 2007 ፕሮግራም

< …በኢትዮጵያ ውስጥ አሁን ያለውን ውጥረት ለማርገብና ለአገሪቱና ለሕዝቡ መፍትሄ ለመፈለግ ቢያንስ እነዚህ ስልጣን ላይ ያሉ ሰዎች በአገርና በሕዝብ ላይ የበለጠ ጉዳት ሳያመጡ የያዙትን ይዘው… አብዮት በማንኛውም ሰዓት ይነሳል የኢትዮጵያ ሕዝብ ግን አሁን ሆ ብሎ አስቀድሞ ያለቀውን ምርጫ ተከትሎ … >

አቶ ፈቃደ ሸዋቀና ስለወቅቱ የኢትዮጵያ ሁኔታ   ለህብር ሬዲዮ ከሰጡት ማብራሪያ የተወሰደ (ሙሉውን ያዳምጡት)

<…በኤርትራ ውስጥ በነጻነት ትንቀሳቀሳላችሁ ወይ ላልከው በነጻነትማ ስለምንቀሳቀስ ነው ይሄው ወጣቶች ትግሉን የሚቀላቀሉበትን ሁኔታ እያመቻቸን ያለነው….አምስት ዓመት ሙሉ ምን ስትሰሩ ነበር የተባለው ወያኔን የመሰለ ጠላት በአንድ ጊዚ ተነስቶ ሳይሆን በቂ ዝግጅት አድርጎ ነው …>

ታጋይ ተፈሪ ካሳሁን በኤርትራ የሚገኘው የአማራ ዲሞክራሲያዊ ሃይል ንቅናቄ መሪ

የቀድሞ የመኢአድ የሕዝብ ግንኙነት ሀላፊን ተስፋሁን አለምነህን ጨምሮ ኤርትራ ከገቡ ሶስት ወጣት ታጋዮች ጋር የተደረገ ቃለ መጠይቅና ያስተላለፉት ጥሪ (ሙሉውን ያዳምጡት)

<…ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ የኢትዮጵያውያን ድጋፍ የነበራቸው እውቅ የህክምና ሰው ፣የህዝብ ተቆርቋሪ አባታቸውን ግራያኒ ገሎባቸው እሳቸው በወያኔ እስር ቤት ተሰቃይተው በወቅቱ ህክምና ተከልክለው ለሞት የበቁ እንደ አቡነ ጴጥሮስ ለአገራቸው ሲሉ የተሰው  ኢትዮጵያዊ ሰማዕት ናቸው …16ተኛ የሙት ዓመታቸውን ስንዘክር በስማቸው ወደፊት ፋውንዴሽን እንዲቋቋምና…>

አቶ ተክሌ የሻው የሞረሽ ወገኔ ሊቀመንበር የፕ/ር አስራት ወልደየስን 16ተኛ የሙት ዓመት መታሰቢያ ዝግጅት ያካሄዱበትን ምክንአት ለህብር በሰጡት ቃል ከገለጹት የተወሰደ(ሙሉውን ያዳምጡት)

የከሸፈው የብሩንዲ መፈንቅለ መንግስት እና በለውጡ አራማጆች ላይ ያመጣው ጣጣ( ልዩ ጥንቅር)

ሌሎችም

ዜናዎቻችን

ደቡብ አፍሪካ የኢትዮጵያውያን ሱቅ ሰሞኑን በዘረኞች ጥቃት ደረሰባቸው በበኬኒያ በስደት ላይ የሚገኙ የኢትዮጵያ ነፃ ፕሬስ ጋዜጠኞች ህይወታቸው አደጋ ላይ መሆኑን ገለጹ

አሜሪካ ዜጎቿ ምርጫውን ተከትሎ በኢትዮጵያ ለሚያደርጉት እንቅስቃሴ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳሰበች

ከመንገድ የታፈኑት አቶ ማሙሸት አማረ ነገ በድጋሚ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ

በሊቢያ ለሞቱት ሐዘን የወጣውን ሕዝብ አሳምጸዋል ተብለው ተከሰዋል

በስልጣን ላይ ያለውን አገዛዝ በአገር ቤትም ሆነ በውጭ በጠመንጃ ብቻ ነው ማንበርከክ የሚቻለው ሲሉ ኤርትራ ለመሳሪያ ትግል የገቡ ወጣቶች ገለጹ

የብሩንዲ ፕሬዝዳንት ህዝቡ ወይ እኔን ወይ አልሸባብን ይምረጥ ሲሉ አስፈራሩ

የኢትዮጵያ በርካታ ወጣቶች ልባቸው መሸፈቱን ሮይተርስ ዘገበ

ናይጄሪያዊው አገረ ገዢ ኢትዮጵያዊት አገቡ መባላቸውን አስተባበሉ

የሚሉና ሌሎችም ዜናዎች አሉን

https://soundcloud.com/hiber-radio-las-vegas-1/hiber-radio-051715-052415

 

 

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *