Hiber Radio: በኢትዮጵያ የስርዓት ለውጥ ካልመጣ ረሃብ ነገም ተመልሶ ይመጣል -ዶ/ር አክሎግ ቢራራ

በኢትዮጵያ ያለው ረሃብ በስልጣን ላይ ያለው አገዛዝ ውጤት ነው የሚል ሙግት ይቀርባል።ድርቅ እአለ ረሃብ የማይከሰትባቸው አገሮች በርካታ ናቸው። የአፍሪካ የዳቦ ቅርጫት በሚል በአንድ ወቅት የምትታወቀው አገራችን ኢትዮጵያ የረሃብ ምሳሌ መሆን ከጀመረች ውሎ አድሯል። ዶ/ር አክሎግ ቢራራ ይህ ስርዓት ስልጣን ከያዘ እንኳ አምስት ረሀብን አስተናግደናል ስርዓቱ ካልተለወጠ ረሃብ ነገም አይቀርልንም ይላሉ። ወገንን መርዳቱ የማይታለፍ የወቅቱ ጉዳይ ኒሆንም ለምን ተራብን? የሚለውን ጥያቄ ካልመለስን ነገም ተመልሰን መራባችን አይቀርም ይላሉ።በወቅታዊው ጉዳይ ላይ የሰጡንን ቃለ መጠይቅ አድምጡት።

የህብር ሬዲዮን ዘገባ ህብር ሬዲዮን ከድህረ ገጻችን በተጨማሪ በስልክ ለማዳመጥ 712 -432-8451 መደወል ብቻ በቂ ነው። በእንግሊዝ ለምትኖሩ በ01405770140 እና በአውስትራሊያ 0280725172 በስልክ ማዳመጥ ይቻላል። ዘወትር በድህረ ገጻችን ወይም ከgoogel store Hiber radio አፕሊኬሽንን ዳውን ሎድ በማድረግና  ከዘሐበሻም ማዳመጥ ይቻላል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *