Hiber radio: ፕ/ት ባራክ ኦባማ የሟቹ ወገናችን ቤተሰቦችን በግንባር ተገኝተው አጽናኑ

Obama_03

በታምሩ ገዳ

የአሜሪካው ፕሪዜዳንት ባራክ ኦባማ በቅርቡ( በታህሳስ 2, 2015 አ. ኤ. አ )በአሜሪካው የካሊፎርኒያ ግዛት በሰምበርላንዲኖ ክፍለ ከተማ ውስጥ ሁለት ባል እና ሚስት አሸባሪዎች የገና በአል ዋዜማን ለማክበር በተሰባሰቡ ሰላማዊ ዜጎች ላይ ባደረሱት ጥቃት አንድ ኤርትራዊ ወገናችንን ጨምሮ 14 ነጹሃን ሰዎች መሞታቸውን እና 21 መቁሰላቸውን ተከትሎ ፕ/ቱ ሰሞኑን የሟቶች ቤተሰቦችን በግንባር ተገኝተው ማጽናናታቸው ታውቋል። ባለፈው አርብ የሟቾች ቤተሰቦችን ለመጎብኘት ወደ ሰንበርላንዲኖ ጎራ ያሉት ኦባማ የሟቾች ቤተሰቦችን ከ አንድ መለሰተና ደረጃ የት/ቤት ቤተ መጽህፍት ውስጥ ለ ሶስት ሰአታት በፈጀ የተናጥል ውይይት “እግዚ አብሔር ያጸናችሁ “ በማለት ሃዘናቸውን ገልጸዋል ። የአክራሪዎቹ ሰለባዎች ከሆኑት መካከል የ60 አመቱ ኤርትራዊው የሆኑት የጤና ጥበቃ ሰራተኛው ኣቶ ይሳቅ እሚኖ የተባሉት ወገናችን ቤተሰቦችን በግንባር ያነጋገሩ ሲሆነ የሟች አቶ ይሳቅ ልጆችን ቀረብ ብለው ያነጋገሩት ኦባማ “እናንተ የይሳቅ ምትኮች (አሻራዎች ) ናችሁ”በማለት አጽናንተዋል።

የአቶ ይሳቅ ወንድም የሆኑት አቶ ሮቤል ተክለ አብ በበኩላቸው ለተለያዩ የዜና ስዎች በሰጡት አሰተያየት “የፕ/ቱ አቀራረብ ቤተሰባችንን ከዚህ ቀደም በአካል የሚያውቁ የመሰል ነበር። ወንድሜ ይሳቅ በሕይወት በነበረበት ወቅት ለፕ/ት ባራክ ኦባማ ልዩ ፍቅር እንደነበረው ይናገር ነበር ። ኦባማ በ2009 እኤአ ለፕ/ትንት ባእለ ሰሜታቸው ላይ እንዲገኝ ወንድሜ የእንግድነት ጥሪ ወረቀት ተልኮለት ነበር። ሰለ ነገ ብዙ መናገር ባልችልም ከፕ/ት ኦባማ ጋር ያደረግነው አጭር ቆይታ በጣም ገንቢ እና አጽናኝ ነበር “ብሏል። እ አኤ አ በ 2000 ለተሻለ ሕይወት ከ ኤርትራ ምድር ወደ አሜሪካ (ካሊፎርኒያ) የተሰደዱት ሟች አቶ ይሳቅ ለ 11 አመታት በጤና መኮንንት ያገለገሉ ሲሆን በ አሁኑ ወቅት የኮሌጅ ተማሪዎች የሆኑት ዮሴፍ፣ ብሩክ እና ሚልካ የተባሉት 3 ልጆቻቸውን በማሳደግ ለወግ ለማእርግ ለማብቃት ደከመኝ ሰለችኝ ሳይሉ ሲጥሩ ሕይወታቸው በድንገት የተቀጩ ታታሪ አባት እንደነበሩ የወንድማቸው /የእህታቸው ልጅ ዛኬ ገ/ኪዳን ያወሷቸዋል። ሴት ልጃቸው ሚልካ ይሳቅ በበኩሏ ሰለወላጅ አባቷ ኣቶ ይሳቅ ስትናገር” አባቴ ርሁሩህ ሰው ነበር ። እናቴን ለምን እንዳገባት ሲነግረኝ አርሷን የመሰለች መለከመልካም እና ጥሩ ሴት ልጅ (ሚሊካን)ለማፈራት ሰለ ፈልግ በማሰብ እንደ ነበር ይመክረኝ ነበር። አባቴ ዛሬ በሁለት እግሮቼ ያለፈረሃት ቆሜ አንድሄድ ያስቻለኝ ታላቅ አባት ነበር። በማለት ሰለአባቷ ለጋሽነት፣ ግልጽነት እና የፍቅር ሰው መሆን ለ ሎሳንጀለስ ታይምስ ጋዜጣ ተናግራለች። ይህ በዚህ እንዳለ የአሜሪካው የፈደራል የምርመራ ቢሮ(FBI) ለአቶ ይሳቅ እና ሌሎች 13 ሰላማዊ ዜጎች ሞት መንሰኤ ናቸው ያላቸው ባል እና ሚስቱ ሳይድ ሪዝዋን ፋሩክ እና ታሽፊን ማሊክ ከመቼ ጀምሮ ወደ አክራሪነት እንደተለወጡ ቁርጥ ያለ መረጃ በማሰባሰብ ላይ መሆናቸው እና መረጃውንም ለማገኘት ከወራት በላይ እንደሚፈጅባቸው ሃሙስ ታህሳስ 24 2015 ለንባብ የበቃው ሎሳንጀለስ ታይምስ ጋዜጣ ዳስሶታል።

የፈርንጆቹን የገና በአልን ከውይት ሃውስ ቤተመንግስታቸው ውጪ ለማክበር ሻንጣቸውን ከመሽንከፋቸው በፊት ከቀዳማዊት እመቤት ሚሺል ኦባማ ጋር ሃዘንተኞችን ለማጽናናት በአካል ሰምበርላንዲኖ ከተማ የተገኙት የ ልእለ ሃያሏ አገር አሜሪካ፣ ፕ/ት ኦባማ ለሁሉም ሃዘንተኛ ቤተሰቦች በጋራ ፣ በአንድነት እና በፍቅር መኖር የአሜሪካ እና የሕዝቧ ታላቁ የባሕል እሴት እንደሆነ እና በዚህም ጊዜ ሁሉም ወገኖች ለዚህ መሰሉ ድርጊት ተግባራዊነት ተግተው እንዲሰሩ ምክራቸውን እና ጥሪያቸውን አሰተላልፈዋል። በተለይ ደግሞ “ላለፉት ሁለት ሺህ አመታት የክርስቶስን መወለድ (የገና በእልን ሲያከብሩ የነበሩ የመካከለኛው ምስራቅ ዜጎች (ኢራቅ እና ሶሪያ) በአሁኑ ወቅት እራሱን የ እስልምና መንግስት እያለ የሚጠራው በአክራሪው ኢይሲስ እየደረሰባቸው ባለው ግድያ እና መዋከብ ሳቢያ የጌታ የአየሱስ ክርስቶስ መወልድን ለማብሰር ደውል እንዳይደወሉ እና ጸሎት እንዳያደርጉ የተገደዱት ክርስቲያኖችን ልናሰባቸው እና ልንጸልይላቸው ይገባል።” ሲሉ በፈርንጆቹ ገና ዋዜማ ሃሙስ እለት ላይ ከጽ/ቤታቸው የላኩት መልክት ያስረዳል።

ህብር ሬዲዮን በህብር ሬዲዮ ድህረ ገጽ ወይም በቀጥታ በስልክ ለማዳመጥ 712 -432-8451 መደወል ብቻ በቂ ነው በእንግሊዝ ለምትኖሩ 01405770140 በስልክ ማዳመጥ ይቻላል። ዘወትር በድህረ ገጻችን፣ googel app store Hiber Radio ወደ ስልክዎ በመጫን ካልሆነም በዘሐበሻ እንዲሁም በተጠቀሱት ስልኮች ማዳመጥ ይቻላል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *