Hiber Radio: ፈረንሳይ ውስጥ በሰደተኞች መካከል በተነሳ ግጭት አንድ ኢትዮጵያዊ ሲሞት ስድስት ቆሰሉ

Ethiopian-calcie-france-003

በታምሩ ገዳ

ፈረንሳይን ከእንግሊዝ በሚያዋስነው የካሊስ ወደብ አካባቢ ከፕላስቲክ ፣ከ ካርቶኖች እና ከቆርቆሮ ቁርጥራቾች የተሰሩ አጅግ ጎስቋላ በሆኑ ኑሮ ደሳሳ ጎጆዎች ውስጥ በሚኖሩ ከኢትዮጵያ፣ከኤርትራ፣ ከሱዳን እና ከመሳሰሉት ከሰሃራ በርሃ በታች ካሉ አገሮች የመጡ ሰደተኞች በአንድ ወገን ከአፍጋኒስታን የመጡ ስደተኞች በሌላ ወገን የተቧደኑበት እና በሰለት ፣ በቆመጥ እና በአጠናዎች በታጀበው ግጭት ሳቢያ የአንድ ኢትዮጵያዊ ሰደተኛ ህይወት ሲጠፋ ስደስት የሚደረሱ መቁሰላቸው ታዋቋል።

የራዲዮ ፍራናስ ኢንተርናሽናል የእንግሊዘኛው ፕሮግራም ከሰፍራው እንደዘገበው ሰኞ አመሻሹ ላይ የህልማቸው ውጥን እና መዳረሻቸውን ወደ እንግሊዝ ለመግባት ጥረት በሚያድረጉት የብለሹ/አምባገነኖች አገዛዞች ፣ የረሃብ እና የደህነት ሰለባዏች ከሆኑት ከምስራቅ አፍሪካ በመጡት ሰደተኞቹ እና በርስ በርስ ጦርነት ከምትታመሰው ከአፍ ጋኒሳታን በመጡት ሰደተኞች መካከል የተነሳው ጸብ እና አምባጓሮ ወደ አካላዊ ጥቃት ተሸጋግሮ ለጊዜው ስሙ ያለተገለጸው ፣ ነገር ግን ከኢትዮጵያ ሳይሰደድ እንዳልቀረ የሚገመተው የ37 አመቱ ሰደተኛ ደረቱ ላይ በቢላዋ ከድረሰበት ጥቃት ሳቢያ በመቁሰሉ በስፍርው ወደ የሚገኝ ሃኪም ቤት ቢወሰድም ሕይወቱን ማትረፍ አለተቻለም ተብሏል። ከዚሁ ግጭት ጋር በተያያዘ ስድስት ኢትዮጵያዊያኖች ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን ከጉዳዩ ጋር በተያያዘም ወደ ሁለት መቶ ሰደትኞች ጎራ ለይተው የተሳተፉ ሲሆን ፖሊስ ጉዳዩን ለማጣራት የሰው እና የቪዲዮ ማስረጃዎችን በማሰባሰብ ላይ መሆኑን ገልጿል።

ወደ እንግሊዝ የሚያሸጋግረውን አውራ ጎዳና ሆነ ዋሻ /ታናልን ቀደሞ ለመቆጣጠር እና በመኪናዎች ወስጥ ተሸሽጎ ለመግባት በሚደረገው እሽቅድምድም እና በአካባቢው ከሶስት ሺህ እስከ ስድስት ሺህ የሚኖሩበትን የካሊሱ ቁጥቋጦ/ጃንግልን በበላይነት ለመቆጣጠር የሚደረገው ፍልሚያ ከዚህ ቀደም በሱዳን ሰደተኞች እና በአፍጋኒስታን ሰደተኞች መካከል መደረጉ የሚታወስ ሲሆን ከአርባ በላይ ሰደተኞች የመቁሰል አደጋ ደረሶባቸው ነበር። ባለፈው ሳምንት እንኳን አንድ ስደተኛ ወደ እንግሊዝ ለመሄድ በመኪና ላይ ሲንጠለጠል ወድቆ ህይወቱ ማለፉ ዘገባዎች የገለጹ ሲሆን ከዚህ ቀደም የ አኢትዮጵያ ፣ከሱዳን ፣ከኤርትራ፣ከሶሪያ ፣ከፍልስጤም ፣ከአፍጋኒስታን ፣ከአኢራቅ ፣ከሞሮኮ እና ከመሳሰሉት አገሮች የመጡ ሰደተኞች በመኪና ፣በፈጣን ባቡር ተገጭተው አሊያም ከባሕር ሰጥመው መሞታቸው ዘገባዎች ያወሳሉ።

የፈረንሳይ መንግስት ባለፈው የካቲት ወር እዚያው ካሊስ ጢሻው አቅራቢያ በሺህ ለሚገመቱ ሰደተኞች ወደ እንግሊዝ ለመሻገር ተስፋ በማድረግ በጊዚያዊ መጠለያነት ይጠቀሙበት የነበረው ደሳሳ ጎጆዎቻቸውን በማፈራረስ ፈረንሳይ ውስጥ የፖለቲካ ጥገኝነት እንዲያገኙ/እንዲያቀርቡ ቢሞክሩም ጥረታቸው ሙሉ በሙሉ ያለመሳካቱ ባለስልጣናቱን የጠቀሱ ዘገባዎች ይናገራሉ።

ህብር ሬድዮን በህብር ሬዲዮ ድህረ ገጽ ወይም በቀጥታ በስልክ ለማዳመጥ 712 -432-8451 መደወል ብቻ በቂ ነው በእንግሊዝ ለምትኖሩ በ01405770140 በስልክ ማዳመጥ ይቻላል። ዘወትር በድህረ ገጻችን፣ ከ googel app store Hiber Radio ወደ ስልክዎ በመጫን ካልሆነም በዘሐበሻ እንዲሁም በተጠቀሱት ስልኮች ማዳመጥ ይቻላል።

 

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *