Hiber Radio: ከሰሜን ጎንደር የአማራ ሕዝብ ትግል አስተባባሪዎች ለምሊሻ ታጣቂዎችና ለመላው የአማራ ሕዝብና ሰላም ወዳድ ኢትዮጵያዊ ወገናችን ሁሉ የተሰጠ አስቸኳይ መግለጫ

amhara-001-killed-metema-hiber-1

ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ሰሞኑን በተደጋጋሚ እንደዛተው የአማራን ክልል የጦርነት ቀጠና አደርጋለሁ ብሎ ተግባራዊ አድርጓል። ንጹሃን የአማራ ተወላጆችን ህጻናትን ጨምሮ ያለርህራሄ ባሰማራው አጋዚ ታጣቂዎች እያስገደለ ይገኛል።የሕዝባዊ ወያኔ መሪዎች የአጋዚ ጦር ብቻ ሳይሆን በሀሰት የገበሬ ታጣቂዎችን ጭምር <<አባይ እንዳይገደብ የሚፈልጉ የሻዕቢያና የኤርትራ ተላላኪዎች ናቸው>> በሚል ወገን ወገኑ ላይ እንዲተኩስ አበል እየከፈሉ መሳሪያ እያስታጠቁ ጭምር አሰማርተዋል። ይሄ ብዙ ርቀት አይወስዳቸውም።ሐቁን የአማራ ምሊሻ ይረዳል።ያውቃል።ሕወሓት በአማራ ሕዝብ ላይ ወልቃይት የአማራ ነው በማለቱ ለሰላማዊ ተቃውሞ የሰጠው የጥይት ምላሽ ሰጥቷል።

ብዙዎቹ የምሊሻ ታጣቂዎች በአገር ሽማግሌ ሐቁ ተነግሯቸው የሕዝባዊ ወያኔ ሐርነት ትግራይን ጸረ አማራ የግፍ ግድያ ተቃውመው ሸሽተው ተመልሰዋል።አንዳንድ ይህን ዓላማ ያልተረዱትን የአካባቢ የአገር ሽማግሌዎችና የሀይማኖት አባቶች፣መላው ሕዝባችን የወያኔ ሐርነት ትግራይ የራሳችንን ንጹሃን የገበሬ ምሊሻ ጭምር ለከፈተው ጸረ አማራ ጦርነት እንዳይጠቀም ማሳወቅ ማስጠንቀቅ አለብን።በደባርቅ የተስተዋለው የወያኔ ግልጽ ሴራ ማሳያ ነው:

ይሄ በአማራ ንጹሃን ላይ የተከፈተ ጦርነት መነሻው የወልቃይትን የአማራ ማንነት ክዶ ሕወሓት ወልቃይት የትግራይ ብሎ አስተዳደር ከልሎ ላለፉት ሃአ አምስት ኣመታት ስፍር ቁጥር የሌለው ዘር ፍጅት አድርጓል። ይሄ የወያኔ የጉልበት እርምጃና ሕገ ወጥ ውሳኔ የመተው ወልቃይት ጉዳይ በሕግ እልባት እንዲያገኝና እንዲስተካከል ህዝቡ ወኪል ኮምቴ መርጦ በሰላማዊ መንገድ ያቀረበውን ጥያቄ ወደ ሀይል ግጭት ሆን ብሎ ወያኔ ስለቀየረ ነው። ይሄ ጦርነት ስለ አባይ መገደብ አይደለም። የህዝቡ በዙሃኑ ምሊሻ ወገናችን ዛሬ በአማራ ክልል የተሰማራው አጋዚ አልበቃ ያለው ወያኔ ጥቂቶችን በሀሰት በመደለል የተከፈተው ጦርነት አማራን ለማጥፋት፣ወልቃይትን በጉልበት ወስዶ ለማስቀረትና የአማራን ሕዝብ ረግጦ ለመግዛት ነው።

ልጆችህ ተምረው የበይ ተመልካች እና ስራ አጥ ያደረገ፣ወገኖችህን ራሱ ባመጣው የዘር ፖለቲካ አማራ ስለሆኑ ብቻ ከተለያዩ ክልሎች ያሳደደ ነው።ለመሆኑ ወያኔ ያልሰራው ግፍ የቱ ነው? ይህን ላንተ መዘርዘር ለቀባሪው ማርዳት ነው።

ከወልቃይት የአማራ ማንነት ጥያቄ አስተባባሪዎች መካከል ኮ/ል ደመቀ ዘውዱን ጨምሮ ታጋዮች የነበሩ ደርግን ለመጣል የተዋደቁ እንጂ ወያኔ እንደሚለው የሻዕቢያም ሆነ የግብጽ ተላላኪዎች አይደሉም።አይሆኑምም።

ለዚህ የወያኔ ቅጥፈት ቦታ ሳትሰጥ ዛሬ በአማራ ሕዝብ ላይ ወያኔ ለከፈተው ግልጽ የዘር ማጥፋት ጦርነትን አውግዘህ በወገኖችህ ላይ አትተኩስ።መሳሪያህን ሕዝብ ግደል ብለው ባሰማሩህ ላይ አዙር። ከአጋዚ ጋር እንዳታብር:፡ ሲጠይቁህ የአማራን ሕዝብ እንደ ጠላት ወታደር ሊጨፈጭፉ ከመጡት ጋር አላብርም በል።

ውድ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን በዚህ አጋጣሚ የሕወሓት ዘረኛ አገዛዝ ባለፉት ሃያ አምስት ዓመታት ተራ በተራ ያልረገጠው፣ያልገደለውና ያላስለቀሰው ብዙሃን ሕዘብ የለም።ላለፉት ዘጠኝ ወራት በኦሮሞ ወገኖቻችን ላይ እየተፈጸመ አለው ዘር ማጥፋት፣ ከሸኮ መዠንገር ጭፍጨፋ እስከ ኦጋዴን የዘር እልቂት፣ ከጋምቤላ የአኙዋ ንጹሃን የሁለት ዙር የዘር ፍጅት እስከ ሲዳማ ሕዝብ ላይ ተፈጸመ ግድያ እአሉ ብዙ መዘርዘር ይቻላል:፡ ዛሬም ወህኒ ቤቶች በሺህ የሚቆጠሩ ኢትዮጵአውያን አበሳቸውን ያያሉ። ከትላንት እስከ ዛሬ እየተፈጸመ ያለው የአማራ ግድያ የተግባር ምስክር ነው። ዛሬ በአማራ ሕዝብ ላይ በይፋ ያወጀውን የዘር ማጥፋት እርምጃ አጠናቆ ነገ ወደ ሌላው ወገናችን መዞሩ አይቀርም። ባለፈው በጎንደር ተቃውሞ ወቅት በኦሮሞ ወገኖቻችን ላይ የደረሰውን ግፍ ስንቃወም ፍጹም ወገናዊ በሆነ ተቆርቋሪነት ነው።ዛሬ በአማራ ሕዝብ ላይ ወያኔ ዘምቶበታል። በየትኛውም አካባቢ ያለ ወገናችን ይህን የወያኔ ፋሺስት ስርዓት እርምጃ በአገኘው አጋጣሚ ሁሉ እንዲያወግዝ እንጠይቃለን።

በየአካባቢው የሚገኘው ሰላም እና ለውጥ ናፋቂ ሕዝብ ለመብቱ የሚነሳበት ወሳኝ ወቅት ነው። የሕዝብ ጠላት የሆነውን ወያኔን ማዳከም የሚቻለው በጋራ በተመሳሳይ ወቅት ፋታ የሚነሳ የጋራ ትግል በማድረግ ጭምር ነው።የሕዝቡ መሪዎች በአማራና በኦሮሚያ ክልል እንደተደረገው ይህ ወሳኝ ወቅት ሳያልፍ ተረባርበን ይህን ፋሺስታዊ የወያኔ ስርዓት ለመገርሰስ በበኩላችን የተጠናከረ ትግላችን ይቀጥል።

ሞት ለፋሺስቶች

የአማራ ሕዘብ ከተከፈተበት የዘር ማጥፋት ጦርነት ተባብሮ ያሸንፋል!

amhara-001-killed-metema-hiber-1

 

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *