Breaking News ኢ/ር ይልቃል ጌትነት የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ከአገር እንዳይወጡ ታገዱ

Yilkal  2
ኢ/ር ይልቃል ጌትነት

ኢ/ር ይልቃል ጌትነት የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር በሰሜን አሜሪካ የተለያዩ ከተሞች ፓርቲው ሊያደርገው ላቀደው ስብሰባ ለመገኘትና ከኢትዮጵያውያን ጋር ለመወያየት ዛሬ አዲስ አበባ ኤርፖርት ላይ ከአገር እንዳይወጡ ተከልክለው መመለሳቸውን ከፓርቲው ያገኘነው መረጃ ያስረዳል።

ኢ/ር ይልቃልን ከኤርፖርት የደህነቱ ሰራተኞች ፓስፖርታቸውን ተቀብለው የመለሷቸው ሲሆን ከዚህ ቀደም በተመሳሳይ ከአገር ሊወጡ ሲሉ ፓስፖርታቸውን ቀምተው ከውስጡ ገጽ ቀደው እንደመለሱላቸው ይታወሳል።

የሰማያዊ እና እውነተኛው የአንድነት ፓርቲ የሰሜን አሜሪካ ድጋፍ ሰጪ ማህበራት አማካይነት የተጠራው ስብሰባ በሰሜን አሜሪካ በተለያዩ ከተሞች ይካሄዳል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሀን ከነዚህም በዲሲ፣በቺካጎ፣በቦስተን፣በሲያትል፣በቬጋስና በሌሎች የሚጠቀሱ ሲሆን ኢ/ር ይልቃል በነዚህ ስብሰባዎች ላይ ለመገኘት ነበር ከአገር ሊወጡ የነበረው።

ኢ/ር ይልቃል አስፈላጊውን የጉዞ ሰነድ ያሟሉ ቢሆንም የስርኣቱ የደህንነት ሰራተኞች ፓስፖርታቸውን ከተቀበሉ በሁዋላ ኢሚግሬሺን መጥተህ ጠይቅ በማለት መልሰዋቸዋል።

 

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *