የህብር ሬዲዮ ጥቅምት 26 ቀን 2010 ፕሮግራም
የአማራ ልሂቃን እስከመቼ የአማራን መደራጀት ይገፉታል? አማራ በማንነቱ ላይ ለሚደርስበት ጥቃት የእነሱ ዝምታ ድርሻ አለው ? ከዶ/ር አክሎግ ቢራራ የቀድሞ የዓለም ባንክ አማካሪ ጋር ሰፋ ያለ ውይይት አድርገናል (ቀሪውን አድምጡት)
የአቶ ለማ መገርሳ የባህር ዳር ጉዞ፣የሰሞኑ የብአዴንና የኦህዴድ መሪዎች ኢትዮጵያዊነት ንግግሮች ከጀርባ በማን ይሆን የሚገፉት? የደህነቱ መ/ቤት የቀድሞ ሹም አቶ አያሌው መንገሻ ዛሬም ሰፋ ያሉ ጉዳዮችን አንስተን ተወያይተናል (ያድምጡት)
ጋዜጠኛ ክንፉ አሰፋ በአውሮፓ ለፍርድ ስለቀረበው የቀይ ሽብር ወንጀለኛ የፍርድ ቤቱን ውሎ ከተከታተለ በሁዋላ ከህብር ጋር ያደረገው ቆይታ ያድምጡት
የእንግሊዝ ባለስልጣናትን ያስጨነቁት የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ባለቤት ዛሬም ይናገራሉ፦”በእጅግ አደገኛ ፈተና ውስጥ ነው ያለሁት”ወ/ሮ የምስራች ኃ/ማርያም(ልዩ ጥንቅር)
ሌሎችም
ዜናዎቻችን
ከ40 በላይ ንጹሃን በሁለት ወራት በኢትዮጵያ በደህነቱ ተገለው መጣል፣
የአማራ መደራጀት ላይ የቀረበ ጥሪ፣
የትራምፕ ዲቪን አግዳለሁ ማለት፣
ኦህዴድና ብአዴን በጋራ ኢህአዴግን እንዲያስገድዱ የቀረበ ጥሪ፣
የእንግሊዝ አዲስ ወደ ኢትዮጵያን ለሚሄዱ የወጣ ማስጠንቀቂያ፣
የቀይ ሽብር ወንጀል ተጠርጣሪው የፍርድ ቤት ውሎና፣
የኤርትራውያን የሰሞኑ ተቃውሞና ውዝግብ እና ሌሎችም
ሌሎችም ዜናዎች አሉን
Hiber radio Las Vegas ይህ ህብር ሬድዮ _የወቅታዊ መረጃ ምንጭ ነው። ህብር ሬድዮ በአቤኔዘር ኮሙኒኬሽን ሴንተር እየተዘጋጀ ከላስ ቬጋስ ከተማ፣ ዘወትር ዕሁድ በአካባቢው ሰዓት አቆጣጠር ከምሽቱ 6፤30 ሰዓት እስከ 8 ሰዓት በህብር ሬዲዮ ድህረ ገጽ ወይም በቀጥታ በስልክ ለማዳመጥ 5639993994 ወይም 563999-3988 ወይም 712-432-8451 በመረጡት ቁጥር መደወል ብቻ በቂ ነው በእንግሊዝ ለምትኖሩ በ01405770140 በስልክ ማዳመጥ ይቻላል። ዘወትር በድህረ ገጻችን፣ ከ googel app store Hiber Radio ወደ ስልክዎ በመጫን ካልሆነም በዘሐበሻ እንዲሁም በተጠቀሱት ስልኮች ማዳመጥ ይቻላል።