Hiber Radio በተቃዋሚ ታዛቢዎች ላይ ጥቃት ሲፈጸም መዋሉ፣አገዛዙ ለራሱ የሰጠውን ምርጫ ውጤት ሕዝቡ እንዲቀበለው አፈናው ተጠናክሯል፣በኦሮሚያ አንዳንድ አካባቢዎች ወጣቶች የሕዝብ ድምጽ እንዲከበር ጠየቁ፣ ሰማያዊ ፓርቲ ኢትዮጵያና ኤርትራ በፌዴሬሽን እንዲዋሃዱ መጠየቁ፣ ኬኒያዊው ጠበቃ ኦባማ ልጃቸውን ይዳሩልኝ ከብት እሰጣለሁ ማለቱ፣ኤርትራ ለዜጎቿ ስደት የሰብኣዊ መብት ተሟጋቾችን ወነጀለች ፣ ምርጫውን አስመልክቶ ከአረና የሕዝብ ግንኙነት ሀላፊና ዶ/ር አክሎግ ቢራራ ጋር የተደረገ ቃለ መጠይቅ እና ሌሎችም

habtamu1

የህብር ሬዲዮ የግንቦት 16  ቀን 2007 ፕሮግራም

< …የምርጫው ውጤት አስቀድሞ የተገመተ ገዢው ፓርቲ የፈለገውን ድምጽ ለራሱ የሚሰጥበት የይስሙላ ነው … በአገር ውስጥም በውጭም ያለው ለውጥ እንዲመጣ የሚሰራው ሀይል ግን በአንድነት ፈጣን ውሳኔ መውሰድ አለበት። በአገር ውስጥ አብዮት መቀስቀስ እንዲችል… >

ዶ/ር አክሎግ ቢራራ የአገር ቤቱን የይስሙላ ምርጫ  አስመልክቶ   ለህብር ሬዲዮ ከሰጡት ማብራሪያ የተወሰደ (ሙሉውን ያዳምጡት)

<…በምርጫው ድምጽ መሰረቅን አስመልክቶ ገበሬውም ተማሪውም መምህሩም በአጠቃላይ ሁሉም ተመሳሳይ ግንዛቤ አለው። ድምጼ እንዳይሰረቅ ብሎ ነበር በድፍረት ስቃይ እየደረሰበት ታዛቢ ልሁን  ለው….ተቃዋሚዎች ተባብረው በጋራ የህዝቡን ድምጽ ለማስከበርና አስገድደው ወደ ዲሞክራሲያዊ ስርዓት ለማምጣት መታገል ለባቸው …>

የአረና የሕዝብ ግንኙነት ሀላፊ ወጣት አምዶም ገ/ስላሴ (ከመቀሌ ምርጫውን አስመልቶ ለህብር ሬዲዮ ከሰጠው ማብራሪያ የተወሰደ )

በየመን ያሉ ኢትዮጵያውያን አጣብቂኝ እና የተባበሩት ሀይሎች የአየር ድብደባ ያደረሱት ጉዳቶች(ልዩ ዘገባ)

የኢሳት የገቢ ማሰባሰቢያ በቬጋስ(ከበዓሉ አዘጋጆች አንዱ ጋር የተደረገ ቃለ መጠይቅ)

አስተያየት በአገር ቤቱ ውጤቱ አስቀድሞ የታወቀ ምርጫ ላይ

ሌሎችም

ዜናዎቻችን

የተቃዋሚ የምርጫ ታዛቢዎች ጥቃት ሲፈፀምባቸው ዋለ

አገዛዙ የሕዝቡን ድምጽ ወደጎን አድርጎ ለራሱ የሰጠውን የምርጫ ውጤት ይፋ ለማድረግ ተዘጋጅቷል

ሕዝቡ በተዘረፈው ድምጹ ጉዳይ ተቃውሞ እንዳያቀርብ በሚል የሰብዓዊ ጥሰቱ ቀጥሏል

 

በኦሮሚያ አንዳንድ አካባቢዎች ተማሪዎች የሕዝብ ድምፅ እንዲከበር መጠየቅ ጀምረዋል

በአዲስ አበባ የ17 ዓመቷን ወጣት ሃና ሌላንጎን የደፈሩት ከ17 ዓመት እስከ እድሜ ልክ እስራት ተፈረደባቸው

ኬኒያዊው ጠበቃ ፕሬዝዳንት ኦባማ ልጃቸውን ከዳሩልኝ ለጥሎሽ 50 ከብቶች 70 በጎችና 30 ፍየሎች እሰጣለሁ ማለቱ ተሰማ

የኤርትራ መንግስት ለአገሪቱ ወጣቶች ስድትና ሞት የሰብዓዊ ተሟጋች ድርጅቶች ጭምር ይጠየቃሉ አለ

ኢትዮጵያና ኤርትራ በኮንፊዴሬሽን እንዲዋሃዱ የሰማያዊ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ ጠየቁ

የሔጉ ውሳኔ በአዲስ መልክ እንዲቀየር አንድ ታማኝ  የተቃዋሚ መሪ ገልፀዋል

ሁቨር በኔቫዳ ስራ እንዲጀምር ህጉ ፀደቀ

ስራ ከመጀመሩ በፊት ለተቆጣጣሪው ኩባንያ ማመልከት አለበት ተብሏል

የሚሉና ሌሎችም ዜናዎች አሉ

https://soundcloud.com/hiber-radio-las-vegas-1/hiber-radio-052415-053115

Hiber radio Las Vegas ይህ ህብር ሬድዮ _የወቅታዊ መረጃ ምንጭ ነው። ህብር ሬድዮ በአቤኔዘር ኮሙኒኬሽን ሴንተር እየተዘጋጀ ከላስ ቬጋስ ከተማ፣ ዘወትር ዕሁድ በአካባቢው ሰዓት አቆጣጠር ከምሽቱ 6፤30 ሰዓት እስከ 8 ሰዓት  በቀጥታ በህብር ሬዲዮ ድህረ ገጽና  በስልክ ለማዳመጥ 712 -432-8451 መደወል ብቻ በቂ ነው።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *